Monday, November 18, 2013

ዘመነኛው ቃል « ጥንቆላና ሙስና»

አንዳንድ ጊዜ የዚህ ሰለባ የሚሆኑት ጋዜጠኞች ናቸው ዘመን ያነሳውን ቃል ይዘው አብረው ይነጉዳሉ። ፖለቲከኞች ደግሞ ለታላቁ ተልዕኮአቸው አቅጣጫ መቀየሪያ ያደርጉአቸዋል። « war on terror» የሚለውን ቃል ይዘው ልጓም በሌለው ፈረስ የጋለቡ የአሜሪካ ፖለቲከኞች  የአሜሪካንን የውጭ ፖሊሲ ለሚመጡት አያሌ አመታት እንዴት እንደጎዱት ያስተውሉታል።

የዓለሙስ ይሁን የቤተ ክርስቲያኑ ከየት መጣ። ለቤተ ክርስቲያን አጀንዳ የሚቀርጽላት መልእክት የሚያቀብላት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንጂ የቄሣር ቤተ መንግሥት አልነበረም። አሁን ግን ቃላት ብቻ መልእክቱንም የሚያቀብላት ቄሣር ሆኖአል።

ከሰሞኑ « ሙስና» የቤተ ክርስቲያኒቷ ነገር ያገባኛል ያሉ ድረ ገጾች ሁሉ የሚለፍፉት ነገር ሆኖአል። ቃላት ሲደጋገም ማሰልቸቱ። ከሁሉ በላይ ደግሞ ማጥቂያ ሲሆን ማሳዘኑ። ከሰሞኑን ሐራ ተዋህዶ የተባለው ድረ ገጽ ያወጣው ግን ይህ የቃላት ጋጋታ ወደ የት እንደሚያደርስ ቆም ብለን እንድናስብ አድርጎናል። ድረ ገጹ በየጽሑፉ ሲያለፋው የነበረውን « ተሐድሶ» የሚለውን ቃል ሰሞኑን ጡረታ ከትቶት አዲስ ቃል ይዞ ተነስቶአል። « ሙስና» የሚል። እርሷ በደንብ ሥራ አልሰራችም መሰለኝ ሌላ ተጨማሪ ቃል አምጥቶአል። « ጥንቆላ የሚል። ያወጣውም አቢይ ርእስ እንዲህ የሚል ነው።   ሀገረ ስብከቱ « የመንበረ ጵጵስና ልዩ ጽ/ቤት» እስከ ማቋቋም በደረሱ ሙሰኞችና ጠንቋዮች እየታመሰ ነው በሚል ርእስ ባወጣው ጽሑፍ ጠንቋዮች የሐገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳሳት እየመሩት እንደሆነ ጽፎአል። ለመሆኑ እንዲህ አይነቱ ጽሑፍ የሚጠቅመው ማንን ይሆን????አስተዳደራዊ በደል ሰርተዋል ያስኬዳል። ነገር ግን የፖለቲካውም የመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ጥርስ የሚያስገቡ ስሞችን መፈለግ ለምን አስፈለገ። ጠንቋዮች የሉም አይደለም። የጥንቆላ ሥራ ትዝ የሚለን እኛ ሰው መደብደብ ሲያምረን መሆን የለበትም።  የራስን ሥልጣን ለማደላደል አገርና ቤተ ክርስቲያን ስንት ጊዜ ትጎዳ፤ ከዚህ የከሳሽ መንፈስስ የሚያወጣን ማን ይሆን?

1 comment:

  1. ከዚህ የከሳሽ መንፈስስ የሚያወጣን ማን ይሆን?this is my question too

    ReplyDelete