Saturday, November 16, 2013

እግዚአብሔር ረሳኝ አትበሉ።

የፈጠረህ የፈጠረሽ፥ ከማኅፀን የተሸከመህ የተሸከመሽ እርሱ ነውና እግዚአብሔር ረሳኝ አትበሉ። ያልተፈጠረውን ቀናችሁን ያልኖራችሁበትን ወራት ያየ ነውና እርሱ ረስቶኛል አትበሉ። በእናታችን ማኅፀን ውስጥ የመገበን እርሱ ነውና ረስቶኛል አትበሉ።

ወደ ብርሃን ያመጣን፥ እስትንፋስን የሰጠን አልረሳንም።
በእናታችን ጫንቃ ላይ ምቾት የሆነን አልረሳንም።
ያቆመን አንደበት የሆነን አልረሳንም።
ያሳደገን በበረከት የመረቀን አልረሳንም።
ለምኞታችን ለክፋታችን ያልሰጠን አልረሳንም።
አልረሳንም።

ፈጥሮ
መግቦ
አቁሞ
አሳድጎ
መክሮ
ሰው አድርጎ
ለዚህች ቀን አድርሶናልና ረስቶናል አትበሉ።

ቀኑ ቢጨልምም አይረሳንም።
በሐዘናችን ቀን እንኳ አይረሳንም።
አቅጣጫ የጠፋን ሲመስለን አይረሳንም
ለጥያቄዎቻችን መልስ ባይኖረን አይረሳንም።
« እናት የወለደችውን ልጅ ልትረሳ ትችል ይሆናል እኔ ግን አልረሳችሁም» ብሎአልናል።
« አልረሳህም ከቶም አልጥልህም» ብሎአልና።



No comments:

Post a Comment