Tuesday, November 12, 2013

አዘክሪ ኵሎ


ታላቁ ባለቅኔና ደራሲ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ፥ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ልጇ ወዳጇን ይዛ በስደት ወደ ምድረ ግብጽ መሄዷን አነጻጽሮ በፋሽሽት ጣልያን ለስደትና ለስቃይ የተዳረጉትን እያሰበ የተቀኘው ቅኔ ሰሞኑን በስደት ዓለም ሳሉ ሕይወታቸው በስቃይ ላይ ያሉትን ወገኖቻችንን የበለጠ የምናስብበት ይሆናል። ዘመኑም የጌታችንን ከእናቱ ጋር ስደት የምናስብበት ስለሆነ፤ አሁንም ወገኖቻችንን ወደ አገራቸው በሰላም ያግባልን። 

ድንግል ሀገሬ ሆይ ጥንተ ተደንግሎ
ሕፃናቱም ታርደው ያንቺም ልብ ቆስሎ
ልጅሽ ተሰደደ አንቺን ተከትሎ፣
የሕፃናቱን ደም አዘክሪ ኩሎ፡፡
አስጨነቀኝ ስደትሺ፣
እመቤቴ ተመለሺ፣ ተመለሺ…

No comments:

Post a Comment