Thursday, November 14, 2013

የስምዖን ዓምዳዊ ጸሎት (ካለፈው የቀጠለ

ምዕራፍ፵፪። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ያች ደም ይፈሳት የነበረችው ሴት የልብስህን ዘርፍ በዳሠሠች ጊዜ በጊዜዋ እንደተፈወሰች፥ እንደዚሁ የተናቁና ከንቱ የሆኑ የሚያደክሙ አሳቦች ከነፍሴ ይፈሳሉና፥ አንተ በምሕረትህ ነፍሴን ፈውሳት ፤ አምላካዊ የሆኑ አሳቦችና የተሠወሩ ምሥጢራት ያድሩባት ዘንድ የሕይወትን ምንጭ አንተ በውስጡዋ አስቀምጥ። 

ምዕራፍ፵፫። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ከኃጢአት መልእክተኛ ከሆዱ ምንጭ አድነኝ። የማትመረመረውንና ከመታወቅ ያለፈችውን የምሥጢራትህን ወንዝ በውስጤ አፍልቅ። በአንተ ሕያው ልሁን፤ በአንተ ልቀደስ፤ አንተ የቅዱሳን ቅዱስ ነህና። 


ምዕራፍ፵፪። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥መፃጕዕን ለመፈወስ ወደበጎች መተላለፊያ የመጣህ፥ ቅዱስ ስለሆነው ስምህ ከኃጢአት፥ ከበደልና ከሐኬት አንካሳነት ፈውሰኝ፤ ከሕመም አልጋም አድነኝ። ከአንተ ዘንድ የሚሆነውን ኃይልህን ስጠኝ በምሕረትህም ፈውሰኝ። ( ይቀጥላል)  

No comments:

Post a Comment