Tuesday, November 19, 2013

ጸሎተ ስምዖን ዓምዳዊ

ምዕራፍ ፵፭ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ እጁ የሰለለችበትን ሰው እንደፈወስከው፥ ልቡናዬን ፈውሰው፥ ፍቅርህን እንዳስተውል አድርገን። አንተ ሕይወትና ፈውስ ነህና። 
ምዕራፍ ፵፮ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ደቀ መዛሙርትህን ከባሕር ማዕበልና ጽኑ ከሆነ ሞገድ ያዳንካቸው፤ በአንተ እድን ዘንድ ዘንድ፥ ክፉዎች ከሆኑ መታወክና መደንገጥ አድነኝ። በአንተ ለሚያርፉ ደካሞች ሁሉ ፥ ወደብና መጠጊያ ነህና። 
ምዕራፍ ፵፯ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ሕይወትንና ዕረፍትን አገኝ ዘንድ፥ በፍቅርህ ገመድ ለዘለዓለም እሰረኝ። 
ምዕራፍ ፵፰ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ከነአናዊቷ ሴት ወደ አንተ አንደጮኸች፥ አንተም ልመናዋን እንደሰማህ፥ አሁንም ወደአንተ የምጮኸውን እኔን ኃጢአተኛውን ባርያህን ስማኝ። 
ምዕራፍ ፵፱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ከመንገድህ ሊያስወጣኝና ሊያስተኝ ከሚያውከኝ ከሰይጣን ሁከት አድነኝ። 

ምዕራፍ ፶  ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በሃይማኖት ዓለት ላይ አጽናኝ፤ እግሬንም በእርሷ ላይ አቅና፤ በእርሱዋ በፍቅርህ እመላለስ ዘንድ ከአንተም ጋር አንድ እሆን ዘንድ። 

No comments:

Post a Comment