Tuesday, November 12, 2013

ተአምራት በሥራ ገበታ፤ የኤቢሲ ጋዜጠኛ ማሞግራምና ውጤቱ

በጥቂቱም በብዙም ማዳን የሚቻለው እግዚአብሔር አድኅኖቱን የሚያሳይበት መንገድ ብዙ ነው። አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ተአምራቱን የሚያሳየው በዕለት ተግባራችን በምናሳየው ታማኝነት ነው። በዚህ በአሜሪካ የአሜሪካ ዜና ማሰራጫ ድርጅት ( abc) ጋዜጠኛ የሆነችው አሚ ሮባክ አለቃዋ አንድ ነገር እንድታደርግ ይጠይቃታል። የካንሰር ቀንን ምክንያት በማድረግ በሚሊዮን ተመልካቾች ፊት አሚ የጡት ካንሰር ምርመራ ( ማሞግራም) እንድታደርግ ይጠይቃታል። እርሷም እሺ ትላለች፤ ምርመራውን ለGood moring America ካቀረበች በኋላ ዶክተሮች ዱብ እዳ ይነግሩአታል። የጡት ካንሰር በሽተኛ መሆኗን። ሆኖም ግን አስደሳች ነገር ይነግሯታል። ያ በሥራዋ ምክንያት ለቴሌቪዥን ማስታወቂያ ያደረገችው ምርመራ ሕይወቷን አድኖአታል። ምክንያቱም ገና በመጀመሪያ ደረጃው ነበር ካንሰሩን ያገኙት።   አሚ በጻፈችው መጣጥፍ ላይ እንደገለጠችው ይህ በእርሷ ሕይወት ያጋጠማት ድርጊት ለብዙ እህቶች ትምህርት ሆኖ በጊዜ የጡት ምርመራ እንዲያደርጉ እንደሚያነሣሣ ተስፋዋ ነው። እኔ ይህን ተአምር ብዬዋለሁ በእለት ተእለት ሕይወታችን በሚኖረን ታማኝነት የምናገኘው በረከት።

ምንጭ ABC News


No comments:

Post a Comment