Wednesday, November 13, 2013

የግብጽ ክርስቲያኖች ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት የአገሪቱ ፕሬዝደንት ልዩ ፈቃድ እንደሚያስፈልጋቸው የሚገልጠው ሕግ ውድቅ ሆነ

  • ይህ ድርጊት ለዘመናት ሲሠራበት የነበረ ሲሆን አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ሕንጻቸውን ቀለም ለመቀባት ተከልክለው ከዓመታት በላይ አሳልፈው ነበር 

የሙስሊም ወንድማማቾች (muslim brotherhood) መንግሥትን መወገድ ተከትሎ በግብጽ የኦርቶዶክስ ምእመናን ላይ የሚደርሰው ግፍና አፈና እንደቀጠለ ቢሆንም ባለፉት መቶ ዓመታት በግብጽ ክርስቲያኖች ጫንቃ ላይ ተጭኖ የነበረው አንድ ሕግ በመሻሩ በመከራቸው ውስጥ ታላቅ የምሥራች አግኝተዋል። 

ከሃይማኖታዊ መልኩ ይልቅ የፖለቲካ እስልምናን  በሚያራምደው የሙስሊም ወንድማማቾች ድርጅት ጸቅቆ የነበረውን የአገሪቱን ሕገ መንግሥትን አሻሽሎ ሁሉን የአገሪቱን ዜጎች በእኩል ዓይን የሚመለከት ሕገ መንግሥት ለማድረግ  የተሰበሰበው የምሑራን ክፍል ከዚህ በፊት ባሉት መንግሥታትም ለምሳሌ በሆስኒ ሙባረክ ጊዜም ለብዙ ዓመታት ሲሰራበት የነበረውንና ክርስቲያኖችን ለማፈን ዓይነተኛ መሣሪያ የነበረውን ቤተ ክርስቲያንን ለመሥራት የአገሪቱ ፕሬዝደንት ልዩ ፈቃድ ያስፈልጋል የሚለውን ሕግ ከአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሠርዘውታል። በዚህ ሕግ መሠረት እድሳት ለማድረግ ከ50 ዓመት በላይ ፈቃድ ሲጠብቁ የኖሩ አብያተ ክርስቲያናት እንደነበሩ ተጠቅሶአል። አሁን ግን ቤተ ክርስቲያኗ የማንንም ፈቃድ ሳትጠይቅ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን መሥራት ትችላለች። በነገራችን ላይ በዚህ በሰሞኑ የእስላማውያን ቅስቀሳ ከ80 በላይ አብያተ ክርስቲያናት የተቃጠሉ ሲሆን እንደ ግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ግምት ከ20 ሚሊየን ዶላር በላይ ንብረት ወድሞአል። 

በጥልቀት ለማንበብ pravoslavie.ru ይጎብኙ



No comments:

Post a Comment