Tuesday, April 10, 2018

ጸሎት

የአባቶቼ አምላክ፥ አምላከ ቅዱሳን አምላከ አበው ልዑል እግዚአብሔር ሆይ፥ አንተ ከፍ ካሉት ሁሉ በላይ ከፍ ያልህ ነህ፤ ሥራህ ከአእምሮ በላይ ነው። ኃይል ከመነገር በላይ ነው። ኃጢአተኛ እና በደለኛ የሆንኩትን እኔን ልጅህን ልከህ ያዳንከኝ፥ ፍቅርህ እጅግ ድንቅ ነው። የእግዚአብሔር ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ጠላት መሆኔን በልጅነት የቀየርከው፥በራቅኹህ መጠን በፍቅርህ የሳብከኝ፥ ውለታህ ዕለት ዕለት ይታወሰኝ፤ዓለም በአዚሟ እንዳታሳውረኝ፥ መስቀልህ በፊቴ ይሳልብኝ። የሰጠኸኝን፥ በሞትህ ያገኘሁትን መዳኔን በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ እፈጽመው ዘንድ ኃይልን ስጠኝ። አንተ የቅድስና መንፈስ፥ የኃይል መንፈስ ፥ ራስን የመግዛት መንፈስ፥ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፥ ሁለንተናዬን ቀድሰው፤ ሰውነቴ፥ ሥጋ ነፍስ መንፈሴ ያንተ መቅደስ ይሁን። ኃጢአት አያድክመኝ። ዓለም አያዝለኝ። በቃልህ ነፍሴ ሐሴት ታድርግ፤ ካንተ ጋር የሚኖረኝ ጊዜ የደስታዬ ምንጭ ይሁን። አሜን።

No comments:

Post a Comment