Tuesday, November 19, 2013

የምትጮኹት ለማን ነው ለሚሉ ሁሉ . . .

የምንጮኸው የገዛ ወገኖቹን ሰብዓዊ መብት ሳይሰጣቸው ረግጦ ለሚገዛ መንግሥት ባለሥልጣናት አይደለም።
የምንጮኸው ዜጎቹ የሆኑ ሴቶችን መኪና ለመንዳት እንኳ ላልፈቀደላቸውና ይህን አሳብ ያነሡትን የነፃነት ተሟጋቾች እሥር ቤት ለወረወረ መንግሥት አይደለም።
የምንጮኸው ሽብርን በመንግሥት ደረጃ እየፈበረከ በሃይማኖት ስም በየአገሩ ለሚበትን መንግሥት አይደለም።
የምንጮኸው ለታሪክ ምስክር ልንሆን ነው። የትናንት እንግዶቻችን የዛሬ አራጆቻችን እንደሆኑ ለማመልከት ነው።
የምንጮኸው ሰማይ ስሚ ምድር አድምጭ ልንል ነው።
የምንጮኸው ሐዘናችንን ነው። ስለ ወደቀችው፥ ስለተደፈረችው ፥ ስለታረደችው፥ እህታችን ነው።
የምንጮኸው አንድ እንድንሆን፥ በአንድ እንድንቆም፥ በአንድነት እንደ አገር እንድናስብ ነው።
የምንጮኸው በዚህ ሁሉ እግዚአብሔር እንዲታረቀን ነው።

ለታሪክ ምስክር እንሁን፤ 

No comments:

Post a Comment