Thursday, November 14, 2013

እግዚአብሔር የሚከብርበት ክርስቲያናዊ ጋብቻ ባሕርያት




እግዚአብሔር የሚከብርበት ክርስቲያናዊ ጋብቻ የሚከተሉት አምስት ባሕርያት ይኖሩታል። 
  1. የእግዚአብሔር ቃል የኑሮአቸው መመሪያ ነው። « ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው»  በማለት መዝሙረኛው እንደተናገረው፥ ክርስቲያዊ ቤተሰብም በቃሉ በመመራት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያከናውናል። መዝ 119፥105። 
  2. ጸሎት የሕይወታቸው መሠረት ነው።  «እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል።ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል።» በማለት ጌታ እንዳስተማረን ክርስቲያናዊ ቤተሰብ  የማይቻለውን ለእግዚአብሔር እያቅረበ የእግዚአብሔርን ጸጋ ይቀበላል። ማር 11፥23_24። 
  3. ፍቅር የቤታቸው ቋንቋ ነው። «  በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ።» በማለት ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው፥ የክርስቲያናዊ ሕይወታችን ዋና አምድ ፍቅር ነው። በባልና በሚስት መካከል ሊኖረው የሚገባውም ፍቅር በሁኔታዎችና በጥቅም ላይ የተመሠረተ ፍቅር ሳይሆን መሥዋዕታዊ ፍቅር ነው። 1 ቆሮ 13፥1። 
  4. መደማመመጥ የዕለት ምግባቸው ነው። «የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈሩ እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ እግዚአብሔርም አደመጠ፥ ሰማም» በማለት ነቢዩ እንደተናገረው፥ ( ሚልክያስ 3፥ 16 በመደማመጥ ውስጥ ፍቅር ይዳብራል። የተሰበረ ይጠገናል፤ የታመመ ይፈወሳል። እግዚአብሔር ጸሎትን ይሰማል። «ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤ ጸሎታችሁ እንዳይከለከል አብረው ደግሞ የሕይወትን ጸጋ እንደሚወርሱ አድርጋችሁ አክብሩአቸው።» 1 ጴጥሮስ 3፥ 7። 
  5. ደስታ ውበታቸው ነው። የእግዚአብሔር ቃል «ምንጭህ ቡሩክ ይሁን ከጕብዝናህም ሚስት ጋር ደስ ይበልህ።እንደ ተወደደች ዋላ እንደ ተዋበችም ሚዳቋ፥ ጡትዋ ሁልጊዜ ታርካህ፥ በፍቅርዋም ሁልጊዜ ጥገብ።» ምሳሌ 5፥ 18_19። ይላል።  እግዚአብሔር የከበረበት ቤተሰብ ደስተኛ፥ ፈገግተኛና ለዛ ያለው ቤተሰብ ነው። 


No comments:

Post a Comment