Monday, December 31, 2012

ዘመን ሲለወጥ



እጅግ ደስ ከሚያሰኙኝ የልጅነት ትዝታዎቼ መካከል፥ በዕለተ ሰንበት ከወላጅ አባቴ ጋር በመሆን ወደቤተ ክርስቲያን በመሄድ አብሬያቸው የሰናብቱን መዝሙር መቆም ነው። « እግዚኦ ጸወነ ኮንከነ ለትውልደ ትውልድ» አቤቱ ለትውልድ ሁሉ መጠጊያ ሆንክ የሚለው የዳዊት ሃይለ ቃል የመዝሙሩ መክፈቻ ነው። መዝሙር 89፥1። ከልጅነት ዘመኔ ጀምሮ ሁል ጊዜ የሚደንቀኝ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን የዳዊትን ኃይለ ቃል ለምን የመዝሙር ምስጋናዋ መክፈቻ እንዳደረገችው ነበር። 

ሆኖም ግን መዝሙሩን በጥንቃቄ ስመለከት የሚያስተምረውን አስደናቂ ዘላለማዊ እውነት ለመረዳት ቻልኩ። 

በዚህ በሃገረ አሜሪካ 2013 ዓ.እ ለመቀበል በዋዜማው ላይ ሳለን፥ በምዕራቡ ዓለም እንደሚኖሩት እንደማናቸውም ሰዎች 2012 ዓእ መለስ ብዬ ለማየት ሞከርኩ።  ድካሜንና ብርታቴን፤ ስኬቴና ሽንፈቴንም አሰላሰልኩ፤ በዚህ ሁሉ ግን ወደአእምሮዬ ላይ የመጣው ይህ ከልጅነት ጀምሮ አእምሮዬ ላይ የተቀመጠው የመዝሙረ ዳዊት ኃይለ ቃል ነው። « አቤቱ አንተ ለትውልድ ሁሉ መሠረት ሆንክ፤» 

Thursday, December 27, 2012

ጉዞ ወደጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን

ታዋቂ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች የአዲስ ኪዳኗን ቤተ ክርስቲያን እንዴት እንዳገኙ የሚናገር ልብን የሚነካ ዶኩሜንታሪ ፊልም።




Tuesday, December 25, 2012

ልብን የሚነካ የአብሮነት መግለጫ

በዚህ በአገረ አሜሪካ ከሚገኙት ታዋቂ የአሜሪካ ፉት ቦል ቡድኖች መካከል (ሶከሩን አይደለም) አንዱ ኮልት ነው። ታዲያ ከሰሞኑ የአሰልጣኙን በሉኪሚያ ካንሰር መታመም ተከትሎ ሠላሳ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች፥ የዋናውን አሰልጣኝ በኪሞ ቴራፒ ውስጥ ማለፍ ለማበረታት ጸጉራቸውን ተላጭተው ነበር። ከሁሉ ልቤን የነካው ሁለት የቡድኑ አድማቂ (cheerleaders) እህቶች አብረው ጸጉራቸውን መላጨታቸው ነው። ቅዱስ መጽሐፍ «ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚለቅሱም ጋር አልቅሱ።» ይህንን ታላቅ ድርጊት ደግሞ ራሱ ቤዛችንና መድኅናችን አድርጎታል። በኃጢአት ፍላጻ ተነድፎ ለሞት የተሰጠውን የሰው ልጅን ከወደቀበት ሐዘቅት ያድነው ዘንድ፥ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እኛን መስሎአል። የቤተ ክርስቲያን ጥሪዋና ድምጽዋ በውጭ ላሉት ሊደርስ ያልቻለው፥ እኛ « በውስጥ» ያለነው ብዙ ጊዜ የምንጨነቀው ራሳችን ከሌሎች ለመለየት እንጂ ከተጠቁት፥ ከተገፉት፥ ልባቸው ከተሰበረውና ግራ ከገባቸው ጋር አንድ ለማድረግ አይደለም። የኮልት ቡድን አባላት ድርጊት ታላቅ ትምህርት ያስተምረን ይሆን? 

Monday, December 24, 2012

ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ ( አቤቱ ብርሃንህንና ጽድቅህን ላክ።



ድንግል ማርያም ካቴድራል። ሎስ አንጀለስ የተሰበከ። 

የኢንተርኔት ዱሪዬዎችን ( Cyber bullies) በሚመለከት

የዚህ ብሎግ መከፈት ዋና ምክንያት በአዲሱ ሚዲያ በጡመራ መድረክ በመጠቀም ስለቤተ ክርስቲያናችን ማናቸውንም እደግመዋለሁ ማናቸውንም ነገሮች እንድንወያይ ነው። ይህም ከትምህርተ አበነፍስ (Pastoral ministry) ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች የሚነሱትንም ይጨምራል። ከጥቂት ቀናት በፊት በብዙ እህቶች ዘንድ ታላቅ መንፈሳዊ ጥያቄ የሆነውን የተፈጥሮ ግዳጅንና መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት ከቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ለማቅረብ የመጀመሪያውን ከተአምረ ሥላሴ አቅርቤ ነበር። ነገር ግን አንዳንድ የኢንተርኔት ዱሪዬዎች ( Cyber bullies) ራሳቸውን ደብቀው መሳደብ ስለጀመሩ በዚህ ብሎግ ላይ ደንብ ማውጣት ተገድደናል።

1. ይህ አሜሪካ ስለሆነ ለተሳዳቢዎች በስድብ መንፈስ መሳደብ መብታቸው ነው። ሆኖም የሚሰድቡት ስም ጠቅሰው ከሆነ እነሱም ስማቸውን መጥቀስ ማለትም ቢቻል በፌስ ቡክ አካውንታቸው በመግባት አስተያየታቸውን መጻፍ ይገባቸዋል። Anonemous  ሆኖ  የስድብ ነገር አስተያየት መስጠት አይቻልም።

2. አኖኒመስ ሆኖ ስድብ የሚጽፈውን መብቱን ለማፈን ሳይሆን የሌላውን መብት ለመጠበቅ ጽሑፉን እንሰርዘዋለን።

3. በአንድ አከራካሪ ነጥቦች ላይ ሐሳብ ለምትሰጡ ግን ስማችሁን ደብቃችሁ ቢሆን አስተያየት (comment) መስጠት ትችላላችሁ።

በመጨረሻ ግን ክፉ በሆነ አንደበታቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች በመስደብ ራሳቸውን ሊቅና ፈራጅ ያደረጉትን ልብ ይስጥልን። 

Saturday, December 22, 2012

ዘመነ ስብከት እና መልእክቱ

ከጌታ ልደት በፊት ያሉት ሦስቱ እሑዶች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ግጻዌ ( lectionary) መሠረት ስብከት፥ ብርሃንና ኖላዊ ይባላሉ። በእነዚህ ሳምንታት ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ፡ ኅቡዓት የተሰኘውን የቤተ ክርስቲያን የጸሎትና የዜማ ክፍል ታዜማለች። የክርስቶስ ሰው መሆንና በእርሱም ያገኘነውን ክብር የመስቀሉን ክብር የሚያመልክት ዜማ ነው።

ከዚሁም ጋር በእነዚህ ሳምንታት ከዳዊት መዝሙራት ላይ፥ አቤቱ ከዓርያም እጅህን ስደድልን ( መዝ 143፥ 7) ፥ አቤቱ ብርሃንና ጽድቅህን ላክልን ( መዝ 42፥3) የእስራኤል እረኛ ሆይ አድምጥ፥ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ (  መዝ 79፥1) በማለት ከወንጌል ንባብ በፊት በሚዜመው የወንጌል መቅድም (ምስባክ) ላይ እናዜማለን። በወንጌላቱም በነቢያት በሐዋርያት የተሰበከለት ጌታ እንደተገለጠ፥ ይህም በሥጋ የተገለጠው ጌታ የዓለም ብርሃን እንደሆነና ነፍሱን ስለበጎቹ በማኖር በጎቹን ወደሕይወት የሚመራ መልካምና በጎ እረኛ እንደሆነ እናነባለን።

እጅህን ስደድልን . .  ብርሃንን . . . አድምጥ. . . ተገለጥ . . . የሚለው ቃል፥ የቀደሙት ነቢያት  የጌታን በሥጋ መገለጥ በምን ዓይነት ሁኔታ ይጠብቁ እንደነበር የሚያመለክት ነው።

አሁን ጌታ ከተወለደ በኋላ ይህን ዘመነ ስብከት ( Season of Advent) ለምን ሠሩልን የሚል ጥያቄ ላለን ስምዖን ዘዓምድ የጸለየው ጸሎት በቂ መልስ ይሆነናል፤

ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ልደትህን በዋሻ ውስጥ ያደረግህ፥ ምስጋናህ በሰማይና በምድር የመላ ሲሆን  ማደሪያ እንደሌለው ደኃ በግርግም ውስጥ የተኛህ፥ ድንቅ የሆነውን ልደትህን እቀበል ዘንድ፥ ሕሊናዬን ዋሻህ አድርገው። ልቡናዬ የመላእክትን መዝሙርና ምስጋና ይማርና ዛሬ መድኃኔ ዓለም ተወልደ፤ ዛሬ በምሕረቱ የሚያሰማራን፥ እንደፈቃዱም የሚመገበን እረኛ ተወለደልን፤ ዛሬ የሕይወት ኅብስት ተዘጋጀልን ተሰጠን ይበል። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ሕሊናዬን ለምስጋናህ ማደሪያ በረት እንዲሆን አድርገው። ታላቅ የሆነውን ውበትህን ይየው፤ ነፍሴም ሕይወት ሰጪ የሆነውን መዓዛህን ታሽትተው። 

በመሆኑም ይህ ዘመነ ስብከት፥ በሥጋ የተገለጠው አዳኝና መድኃኒት ወደሕይወታችን እጁን እንዲሰድ፥ ብርሃኑን እንዲገልጥልን፥ ጩኸታችንን እንዲያደምጥና በክብር እንዲገለጥ ነው። ከሁሉም በላይ በገናነቱ በጌትነቱና በድንቅ ፍቅሩ በልባችን እንዲወለድ ነው። 

ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ሕሊናዬን ለምስጋና ማደሪያ በረት አድርገው፤ ታላቅ የሆነውን ውበትህን ይየው። አሜን 

Wednesday, December 19, 2012

You have accomplished nothing.

One day, while St Antony was sitting with a certain Abba, a virgin came up and said to the Elder: ‘Abba, I fast six days of the week and I repeat by heart portions of the Old and New Testaments daily.’ To which the Elder replied: ‘Does poverty mean the same to you as
abundance?’ ‘No’, she answered. ‘Or dishonor the same as praise?’ ‘No, Abba.’ Are your enemies the same for you as your friends?’ ‘No’. she replied. At that the wise Elder said to her: ‘Go, get to work, you have accomplished nothing.’ And he was justified in speaking like this. For if she fasted so strictly as to eat only once a week, and then very little, should she not have regarded poverty in the same way as abundance? And if she repeated passages from the Old and New Testaments daily, should she not also have learnt humility? And since she had surrendered everything worldly, should she not have considered all people to be her friends? And if she did still have enemies, could she not learn to treat them as friends after so much ascetic effort? The Elder was quite right when he said, ‘You have accomplished nothing.’

St Peter of Damaskos 

Seeking God in the Present Moment

" Every moment and every event of every man's life on earth plants something in his soul. For just as the wind carries thousands of winged seeds, so each moment brings with it germs of spiritual vitality that come to rest imperceptibly in the minds and wills of men. most of these unnumbered seeds perish and are lost because men are not prepared to receive them: for such seeds as these cannot spring up any where except in the good soil of freedom, spontaneity and love."
Thomas Merton, a Trappist monk. 

ወር አበባና ቅዱስ ቍርባን በተአምረ ሥላሴ

የእብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተአምራታቸው ይህ ነው። በረከታቸው ከእኛ ጋር ይሁን አሜን። 

በአንዲት ዕለት ብዙ ሰዎች ቍርባን ለመቀበል ወደ ወደቤተ ክርስቲያን ሄዱ። ነገር ግን የተቀበሉ ቢመስላቸውም የእግዚእብሔር መላእክት ይከለክሉአቸው ነበር። በዚያች አገር ግን፥ በወር አባባዋ ጊዜ የነበረች አንዲት ሴት ነበረች፥ « ዛሬ በክፉ ምግባሬ ከወንድሞቼ ጋር ቅዱስ ቁርባን እንዳልቀበል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ለዩኝ»  እያለች ታዝን ነበር። ነገር ግን መላእክት ከህዝቡ የወሰዱትን ለዚህች በወር አበባ ላለች ሴት ሲያቀብሉአት አረጋዊ የሆነ አንድ መነኩሴ ተመለከተና በመደነቅ ለሀገሩ ሁሉ ተናገረ። የሰሙት ሕዝብ ሁሉ ስለተደረገው ስለዚህ ነገር እጅግ አደነቁ። ይህም የሆነው በወርኃ ታኅሣሥ ነው።

ምንጭ፡ ዜና ሥላሴ የተባለው የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍ። 

Tuesday, December 18, 2012

የስምዖን ዓምዳዊ ጸሎት ( ክፍል አራት)

ምዕራፍ ፲፩፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በጨርቅ የተጠቀለልክ ኃይልህን ስጠኝ፤ በጥበብህም ጠቢብ አድርገኝ፤ አንተ የሕይወት ጥበብ ነህና። ሕይወትን ሰጪ በሆነው ስምህ ታድነኝ ዘንድ፤ ወደ መዳን ወደብ ትመራኝ ዘንድ እለምንሃለሁ።ብርሃናውያን ( መላእክት) ከአንተ ሕይወትን የሚመገቡ፥  ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ጡቶች ወተትን የጠባህ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ነፍሴ ከአንተ ሕይወትን ትመገብ ዘንድ እለምንሃለሁ። የሁሉ ሕይወት ሆይ ሕያዋን የሆኑ ሁሉ በሕይወት የሚኖሩት በአንተ ነው።  አንተ ከሰማይ የወረደ ለፍጥረት ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ  የሕይወት ኅብስት ነህ። ሕይወትን ስጠኝ በጎ በሆነችውም ፈቃድህ መግበኝ።

ምዕራፍ ፲፪፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥  የአብርሃምን ቤት የተስፋ ማኅተም ለመቀበል፥ በአብርሃም ልጆች ላይ  የወሰንከውን ሕግ ለመፈጸም በስምንተኛው ቀን ወደ ግዝረት ቤት የገባህ፥ ቅድስት በምትሆን በሥላሴ ማኅተምኅ ልቡናዬን አትመኝ። ።ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በመንፈስህ ሰይፍ ግዘረኝ፤ የጨለማ ኃጢአት የሆነችውን ሸለፈት ከእኔ  ቁረጥልኝ።

ምዕራፍ ፲፫፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ እኔ በምድር ላይ እሳትን ልጥል መጥቻለሁ እንድትነድም እፈልጋለሁ ያልክ፥ በእርሷ እነጻባት ዘንድ  በልቤ ውስጥ ትንደድ። ለአንተ ንጹሕና ቅዱስ ማደሪያ ይሆን ዘንድ ልቤንና ሕሊናዬን አንድ ታድርግልኝ። ሕይወትን በሚሰጥ በስምህ አንጻኝ፤ ሕይወትን ያፈልቅ ዘንድ የሕሊናየን ውስጥ አትመው። ስምህ የሕይወት ወንዝ ነውና፤ በውስጡ ስምህ ያለው ነፍስ ሁሉ በሕይወት ይኖራልና። 

Monday, December 17, 2012

የስምዖን ዓምዳዊ ጸሎት (ክፍል ሦስት)

ምዕራፍ ፰፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ  ሆይ ፥ ሁሉን በማኅፀን የምታበጅ ስትሆን በማኅፀን የተሣልክ፥ ከአባትህና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በኩነታት ያለህ፥ አዲስ ዕቃ እንድሆንና ፈቃድህን ማድረግ እችል ዘንድ በውስጤ ጸጋህን ሳልብኝ። በአንተ እድን ዘንድ ሕይወትንም አገኝ ዘንድ፥ አዲሱን ወይንህን በውስጤ አፍስስ። 

ምዕራፍ ፱፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ከዓለም አስቀድሞ  የአብ ልጅ ስትሆን በሥጋዊ ልደት የተወለድክ፥ አንተን እመስል ዘንድ በመንፈሳዊ ልደት ውለደኝ። 

ምዕራፍ ፲፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ልደትህን በዋሻ ውስጥ ያደረግህ፥ ምስጋናህ በሰማይና በምድር የመላ ሲሆን  ማደሪያ እንደሌለው ደኃ በግርግም ውስጥ የተኛህ፥ ድንቅ የሆነውን ልደትህን እቀበል ዘንድ፥ ሕሊናዬን ዋሻህ አድርገው። ልቡናዬ የመላእክትን መዝሙርና ምስጋና ይማርና ዛሬ መድኃኔ ዓለም ተወልደ፤ ዛሬ በምሕረቱ የሚያሰማራን፥ እንደፈቃዱም የሚመገበን እረኛ ተወለደልን፤ ዛሬ የሕይወት ኅብስት ተዘጋጀልን ተሰጠን ይበል። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ሕሊናዬን ለምስጋናህ ማደሪያ በረት እንዲሆን አድርገው። ታላቅ የሆነውን ውበትህን ይየው፤ ነፍሴም ሕይወት ሰጪ የሆነውን መዓዛህን ታሽትተው።  ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ሕይወት ሰጪ በሆነው በስምህ እርዳኝ፤ ጽኑዕ በሆነው በእጅህም መግበኝ። 


Sunday, December 16, 2012

የስምዖን ዓምዳዊ ጸሎት (ክፍል ሁለት)



ምዕራፍ ፬፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ የእጅህ ሥራ በሙስና ወድቆ ባየህ ጊዜ፥ ልትመልሰውና፥ ዳግመኛ በቸርነትህ ልታድሰው ርኅራኄህን በላዩ አደረግህ። ከትእዛዝህ በመራቁ በሞት ማኅፀን ውስጥ የገባውን ሰውን ታድነው ዘንድ፥ በማኅፀን አደርክ። በርጉም ሰይጣን አሳችነት፥ አዳም በደለ። ትእዛዝህንም ሻረ። አንተ ግን በምሕረትህ አዳንከው፤ በይቅርታህም ድቀት በሌለው መነሣት አነሣኸው።

ምዕራፍ ፭፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ምጽአትህንና በሰው ልጅ ሥጋ ማደርህን ያውጅ ዘንድ ገብርኤልን የላክኸው፥ አንተን ደስ ለሚያሰኝ በጎ ምግባር ሁሉ የተዘጋጀሁ እሆን ዘንድ፥ ከአንተ የሆነውን ኃይልህን በውስጤ አሳድር።

ምዕራፍ ፮፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ወደሚታየው ወደዚህ ዓለም የወርድህ፥ የመንፈሳውያንን አምልኮ እማር ዘንድ፥ በምስጋናቸው አመሰግንህ ዘንድ በቡራኬያቸው እባርክህ ዘንድ፥ ወደ ልቡናዊት ማደሪያህ ከፍ ከፍ አድርገኝ። ይህንን በጸጋ ከአንተ ስጠኝ፤ እንደፈቃድህም መግበኝ፥

ምዕራፍ ፯፡ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ሥውር ከሆነው እቅፍና ቦታ መጣህ። በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ማኅፀን አደርክ። ይህችውም መንፈስ ቅዱስ የቀደሳትና መቅደሱ ያደረጋት፥  የሰው ፍጥረት መመኪያ ናት። አሁንም በልቡናዬ ታድር ዘንድ ከልዑላውያን ጋር አመሰግን ዘንድ ከአምልኮአቸው ጋር እተባበር ዘንድ ፥ ልቡናዬን ወደ ሥውሩ ማደሪያህ ከፍ ከፍ አድርገው። 

የስምዖን ዓምዳዊ ጸሎት (ክፍል አንድ)



ምዕራፍ ፩፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በፊቴ የሕይወትን በር ክፈትልኝ። አንተ የሕይወትና የድኅነት በር ነህ፤ የሚያገኝህ በውስጣዊ ሰውነቱ ሕይወትን ያገኛል። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ንጹሑን የእግርህን ተረከዝ ታቅፈው ዘንድ፥ በእንባዋ ነጠብጣብ ታርሰው ዘንድ፥ ከእርሱም የሕይወትን መዓዛ ታሸት ዘንድ ለነፍሴ ስጣት። ለዓለማት ሕይወትን የምትሰጥ ፈውሰኝ፤ ፈቃድህን እንድፈጽም የበቃሁ አድርገኝ። የምትመግበኝ የአንተ ፈቃድ እንጂ የእኔ ፈቃድ አይሁን። ስለ እኛ በላከህ በአብ፥ ወደኛ ባወረደህ በፍቅርህ፥ ሥራዎችን ሁሉ በምታከናውንበትና በምትቀድስበት በመንፈስ ቅዱስ እለምንሃለሁ። ከአእምሮ በላይ በሆኑ ምሥጢራትህ  የተሞላ፥ ንጹህና ቅዱስ መቅደስህ እሆን ዘንድ፥ በነፍሴና በሥጋዬ፥ በልቡናዬና በሕሊናዬ ቅድስናን ስጠኝ፤በወለደችህ፥ በእመቤታችን ማርያም እለምንሃለሁ፤ በተሸከመችህ ማኅፀን፥ በተሸከሙህ ጉልበቶች፥ ባቀፉህ ክንዶችህ፥ ባጠቡህ ጡቶች፥ ለእኔም ለኃጢአተኛው መጋቢ ረዳትና ጠባቂ ሁን አሜን።

ምዕራፍ ፪፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የሚለምኑህን ተስፋቸውን የማታሳፍር፥ መምጣትህን ስለተነበዩ ስለነቢያት፥ ወንጌልህን ስለሰበኩ ስለሐዋርያት፥ በፊትህ ሥጦታ ሆኖ ተቀባይነት ስላገኘ ስለ ሰማዕታት ደም፥ በየገዳማቱና በየበዓታቱ ወድቀው ስላሉ አባቶች እንባ  እለምንሃለሁ፤ መሪዬ ሁነኝ፤ መንገዴን አቅናልኝ፤

ምዕራፍ ፫፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በማኅፀን የሠራኸኝ፤ መሪና አዳኝ ሁነኝ። 

Saturday, December 15, 2012

ቃልና ተግባር በቤተሰብ ሕይወት ውስጥ





በእድሜ እየበሰልኩ ስመጣ፥ ሰዎች ለሚናገሩት ነገር ትኩረት አልሰጥም፤ ለሚያደርጉት እንጂ። 
አንድሪው ካርኒጌ 


በማናቸውም ቀን ስብከት ከመስማት ይልቅ ማየት እወዳለሁ። 
ኤድጋር ገስት 

ልጆች ከቤተሰቦቻቸው የሚቀስሙትን ታላላቅ እውነታዎች የሚረከቡት፥ በንግግር  ወይም በጽሑፍ ሳይሆን በማየት ነው። እንዲያውም ከአባት ከእናት ወደልጅ የሚተላለፉ እሴቶችን በንግግር መግለጽ ወይም በጽሑፍ መገልጥ አዳጋች ነው። የእናትን ፍቅር ወይም የአባትን ምቾት ማን ይገልጠዋል? ቃላትን በመቅረጽ ባለሙያዎች ለሆኑት ባለቅኔዎችና ጸሐፍት እንኳ ይህ ታላቅ ተግባር ነው።

ምዕራቡ ዓለም የመቻቻል መንፈስ ብዙ የሚደሰኮርበት ስለሆነ ብዙዎች በቃላቸው ሰውን እንዳይጎዱ በጣም የሚጠነቀቁበት ዓለም ነው። በልምምድ የተገኘ ከሚመስለው ፈገግታ ጀምሮ ሐሰተኛ እስከሆነው ትህትና ድረስ፥  የሰውን ጓደኝነት መግዣ መንገዶች ተደርገው በመወሰዳቸው፥ እውነተኛ የሆነ ውይይት ለመፍጠርና የልብ ጓደኛ ለማግኘት ከባድ ነው። ይህ የኑሮ ፈሊጥ ወደቤተሳባዊ ሕይወት ዘልቆ ከመግባቱ የተነሣ፥ በአባትና በልጅ ወይም በእናት እና በልጅ መካከል ያለው ቅርርብ ከልብ ያይደለ ከስሜት የራቀና ባዶ ሆኖ እናገኘዋለን።

በመሆኑም በዚህ ዘመን ልጆች ወላጆቻቸውን ከሚኮንኑበት ነገር አንዱ ግብዝነት የሆነውም ለዚህ ነው። ግብዝነት ምንድነው ብለን ስንጠይቅ ቃልና ተግባር ያልተዋሃዱበት መንታ ሕይወት ማለት ነው። የወንጌሉን ቃል ከወሰድን፥ ግብዝነት ከእግዚአብሔር መንግሥት የሚከለክለን ሕይወት ነው። ማለት በሌላ መልኩ በልጆችና በወላጆች፥ ወይም በሕይወት አጋሮች፥ ወይም በጓደኞች መካከል እውነተኛ የሆነ የፍቅርና የእውነት ሕይወት እንዳይኖረን የሚያደርግ ነው።

በቤተሰብ መካከል ሊኖር ስለሚገባው መንፈሳዊ ሕይወት ስንነጋገርም፥ የምናገኘው ከዚህ የራቀ አይደለም። ለምሳሌ በዲያስፖራ ባለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጎልተው ከሚታዩት ጥያቄዎች መካከል፥ ክርስትናችንን ለቀጣይ ትውልድ እንዴት ማስተላለፍ አለብን የሚለው ነው። በቤተ ክርስቲያን አደባባዮች ስለልጆቻችን የሚነገሩት ቃላት ትርጕም የለሽ ሆነው ተንነው የሚቀሩት፥ ንግግራችን ከተግባራችን ጋር የተቀራረበ ባለመሆኑ ነው። ወላጆች ለልጆቻቸው መንፈሳዊ ሕይወትን ለማስተላለፍ የተሰጠ ሕይወት አላቸው ወይ? ከልጆቻቸው ጋር አብረው ይጸልያሉ?  ለልጆቻቸው ቃለ እግዚአብሔር ያነቡላቸዋል? ወላጆች የዕለት ችግሮቻቸውን ወይም ከሰዎች ጋር ያላቸውን ግጭቶች ሲፈቱ፥ መንፈሳዊ እሴቶችን የኑሮአቸው መመዘኛ ያደርጋሉ? እነዚህ ነገሮች በልጆቻችን ዓይን ፊት የክርስትናችን መስፈርቶች ናቸው።  ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ታላቅነት ብንተርክላቸው፥ ልጆቻችን የሚመለከቱት የእኛን መንፈሳዊ ሕይወት መሠረት ነው።

አንድ ባልንጀራዬ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ካህን ጻፉት ብሎ የነገረኝ ይህን እውነታ ያጸናልናል።  ወላጆች ለልጆቻቸው እምነት ማጣት ምን ያህል ምክንያት እንደሚሆኑ ሲናገሩ  « ብዙዎች ልጆች እግዚአብሔር የለሽ የሚሆኑት ከቤተ ክርስቲያን ሲመለሱ  እሁድ ጠዋት ነው» ብለው ነበር ።  ወላጆች አብረው በአምልኮ የተሳተፉትን ወገኖቻቸውን ስም ጠርተው በሐሜት ሲያነሱዋቸው፥ ወይምየካህኑን ስብከት ሲያጣጥሉ የሃይማኖት አባት የሆነውን ካህን በንቀት ሲያጣጥሉት፥  ከቅዳሴው ውበት ይልቅ የቤተ ክርስቲያን ፖለቲካና አተካራ የንግግራቸው ማዕከል ሲሆን፥ ልጆች ያዳምጣሉ። ያዳምጡና የወላጆቻቸውን ቃልና ተግባር ይመዝናሉ። ወላጆቻቸውን ይመዝናሉ ቀልለውም ያገኙአቸዋል። እግዚአብሔር በጸጋው ካልሰወራቸው የወላጆቻቸውን የለብታ ሕይወት በማየት << ክርስትና እውነተኛ ሕይወት (authentic life) የማይሰጥ በግብዞች የተሞላ እምነት ነው>>  ብለው ከቤተ ክርስቲያን ይርቃሉ። በአሁኑ ወቅት በቤተ ክርስቲያን ላይ ያለው ታላቅ ክስም ይህ የሆነው ለዚህ ነው።