Sunday, November 17, 2013

ከቅዳሴ መልስ፤ « ስደት እስከ መቼ? »

በዛሬው ዕለት በእግዚአብሔር ቸርነት ቃለ እግዚአብሔርን ያስተማሩን ኦርቶዶክሳዊው ሰባኬ ወንጌል አባ ወንጌል አያልነህ ነበሩ። ሐዲስ ሐዋርያ አባ ወልደ ትንሣኤ « ስደት እስከ መቼ?» በሚል ርእስ ባስተማሩት ትምህርት ዮሴፍ በመልአከ እግዚአብሔር በተነገረው መሠረት ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያምንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዞ ወደ ናዝሬት መመለሱን፤ ይህም የሆነው የሕፃኑን ነፍስ የሚፈልገው ሄሮድስ በመሞቱ እንደሆነ ገልጠዋል።

በመሆኑም ስደት የሚያበቃው ለስደት ምክንያት የሆነው ነገር ሲወገድ እንደሆነ በማብራራት፥ ዛሬ ለእኅቶቻችንና ለወንድሞቻችን ሰቆቃ ምክንያት የሆነው ስደት ምክንያቶች ብዙዎች እንደሆኑና እነርሱን ለማስወገድ በአንድነት ማሰብ እንዳለብን አስተምረውናል።

ለእመቤታችንና ለልጅዋ ስደት ምክንያት የሆነው ሄሮድስ ነበር። ሄሮድስ በፍቅረ ሲመት ዓይኑ ታውሮ፥ ገና አድጎ መንግሥቴን ይቀናቀናል ብሎ ስለጠረጠረ ጌታን ለመግደል ፈለገ። የቤተ ልሔም ሕፃናትንም አስገደለ። ፍቅረ ሲመት (የሹመት ፍቅር) አደገኛ ነገር ነው። ያሳውራል ያሳብዳል፤ ደም እስከማፍሰስ ያደርሳል። በዚህ የወደቁት የፖለቲካ ሰዎች ብቻ አይደሉም። ዛሬ ዛሬ እንደምናየው ጳጳሳቱና ካህናቱ ሁሉ ሳይቀሩ በዚህ ወድቀዋል ብለዋል።

ሐዲስ ሐዋርያ በዚህ ሳያቆሙ ሄሮድሳዊ ሕይወት ስንይዝ ከውስጣችን የሚሰደዱ ብዙ ነገሮች እንደሚኖሩና ከእነዚህም መካከል አንዱ የሆነው የሥጋ ወደሙ ሕይወት ከብዙዎቻችን ሕይወት እንደተሰደደ በማስታወስ ዛሬ ክርስቶስ በልባችን እንዲነግሥና እኛም የሥጋ ወደሙ ሕይወት እንዲኖረን አሳስበውናል። 

4 comments:

  1. thank you for sharing this, those of us whom serve beneath and above the congregational space rarely receive the blessing of this wisdom

    ReplyDelete
  2. Thank you for sharing, Amen.

    ReplyDelete
  3. እድሚና ጤና ለኒሕ ብርቅየ አባት።



    ReplyDelete
  4. kale heywet yasemalen

    ReplyDelete