Saturday, November 16, 2013

በእግዚአብሔር ፊት ስንቆም

በሩቅም በቅርብም ያለን በዕለተ ሰንበት በእግዚአብሔር ፊት እንቆማለን። በዚህ ወቅት የሚከተሉትን ነገሮች እናስብ። 

 
በዳዊት መዝሙር 136 እንደምናገኘው በባቢሎን ምርኮ የነበሩት ኢየሩሳሌምን ባሰቡ ወቅት በእንባ ፊታቸው ተሸፍኖ ሀገራቸውን ላይረሱ « ኢየሩሳሌ ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ»  ቃል ገብተዋል። 

ለእኛም ይህ ዕለት በችግር ያሉትን እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን ላለመርሳት ቃል የምንገባበት ጊዜ ይሁንልን። 
 ይህ ዕለት በችግር ያሉትን እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን በጸሎት ለማሰብ ቃል የምንገባበት ጊዜ ይሁንልን። 
ይህ ዕለት የእህቶቻችንንና የወንድሞቻችንን ሥቃይ ተመልክተን በፍቅር በአንድነት በይቅርታ የምንቆምበት ጊዜ ይሁንልን። 

1 comment: