Friday, June 28, 2013

ጸሎተ ስምዖን ዓምዳዊ (ክፍል 13)

ምዕራፍ፴፱። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ለጠፋው በግ ያዘንክለት፥ በትከሻህ ላይ የተሸከምከው፤ ወደ በጎችህ ማደሪያ ያገባኸው እኔንም ከበጎችህ ቍጥር አንድ አድርገኝ፤ ቃልህን ከሚሰሙ፥ ትምህርትህንም በሥራ ከሚገልጡትና በማኅተምህ ከታተሙት ጋር አንድ አድርገኝ፤

ምዕራፍ፵። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በፍጹም ልቤና በኅሊናዬ እከተልህ ዘንድ ፈቃድህን ከሚያደርጉ ጋር አንድ አድርገኝ፤ አንተ የሕይወት በር ነህና፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ሕይወት ሰጪ ወደሆነች አደባባይህ እገባ ዘንድ በርህን ክፈትልኝ።

ምዕራፍ፵፩። ቸር እረኛ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ርኅራኄህ በእኔ ላይ ይሁን፤ እኔን ባሪያህን በምሕረትህ ፈውሰኝ፤ እኔ በወንበዴዎች መካከል የወደቅኹ፤ ያቆሰሉኝና ጥላቻን የጨመሩብኝ ነኝ፤ ቸር እረኛ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፥ ቍስሎቼን ፈውስ፥ በእኔም ላይ ከወይኑ፥ ከዘይቱና ከቅቡ አፍስስብኝ፤ በምሕረትህ ተሸከመኝ፤ አንጻኝ፥ ሕይወት ሰጪ ወደሆነችው ማደሪያህ አግባኝ፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ተኩላዎች አቆሰሉኝ፤ በጥርሳቸውም ነከሱኝ፤ አንተ ግን በምሕረትህ ከእነርሱ አድነኝ። አንተ ቸር እረኛ ነህና። አሜን (ይቀጥላል።  

1 comment:

  1. betam amesegenalhu, yhe tslote betam des asegntognal, ebakehen hulunem tolo post adregew, weyem demo menchun tekeselen!!!!!!!!!!!!!!

    ReplyDelete