Thursday, June 20, 2013

ጸሎተ ስምዖን ዓምዳዊ (ክፍል 12

ምዕራፍ ፴፪፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በገዳም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት የጾምክ፤ ከፈታኙ ዘንድ የተፈተንክ፥ ፈተናውንና ክፋቱን  ሁሉ ድል ያደረግህ፤ ከአንተ ዘንድ ረድኤትንና ድል ማድረግን ስጠኝ፤ ወደ መንፈሳዊ ተጋድሎና ምስክርነት ለተጓዘ ሰው፥ አንተ ከእርሱ ጋር ትሆናለህ፤ ድል አድራጊነትንም ትሰጠዋለህ።

ምዕራፍ፴፫፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ የጨለማ አለቃ የሆነው ዲያብሎስ የጻፋትን የኃጢአትን ሥርዓት ከሕሊናዬና ከልቤ ደምስስልኝ፤ ቅዱስና አምላካዊ የሆነውን የአንተን ሥርዓት በኅሊናዬ ውስጥ እንዲገባ በሰውነቴ ውስጥ ጻፈው፤ ከልቤ ጋር ከሚዋጋው ከክፉም አድነኝ።

ምዕራፍ፴፭፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ የክፉውን የዲያብሎስን ኃይል የሰበርክበትን ኃይህን ስጠኝ፤ አንተን ደስ አሰኝበት ዘንድ በጥበብህ አስተዋይ አድርገኝ። ስለ ቅዱስ ስምህ ስትል ይህን ኃይልህን እንዲያው በፀጋህ ስጠኝ። ኅሊናዬ ሆይ ለዓለማት ሕይወት ከሚሰጥ ጌታ ጋር ሁን፤ ለራስህ ሕይወትን ታገኝ ዘንድ ተከተለው። ከእርሱ ጋር ወደ ቃና ዘገሊላው ሠርግ ተሻገር። አሜን (ይቀጥላል።) 

No comments:

Post a Comment