Monday, December 24, 2012

የኢንተርኔት ዱሪዬዎችን ( Cyber bullies) በሚመለከት

የዚህ ብሎግ መከፈት ዋና ምክንያት በአዲሱ ሚዲያ በጡመራ መድረክ በመጠቀም ስለቤተ ክርስቲያናችን ማናቸውንም እደግመዋለሁ ማናቸውንም ነገሮች እንድንወያይ ነው። ይህም ከትምህርተ አበነፍስ (Pastoral ministry) ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች የሚነሱትንም ይጨምራል። ከጥቂት ቀናት በፊት በብዙ እህቶች ዘንድ ታላቅ መንፈሳዊ ጥያቄ የሆነውን የተፈጥሮ ግዳጅንና መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት ከቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ለማቅረብ የመጀመሪያውን ከተአምረ ሥላሴ አቅርቤ ነበር። ነገር ግን አንዳንድ የኢንተርኔት ዱሪዬዎች ( Cyber bullies) ራሳቸውን ደብቀው መሳደብ ስለጀመሩ በዚህ ብሎግ ላይ ደንብ ማውጣት ተገድደናል።

1. ይህ አሜሪካ ስለሆነ ለተሳዳቢዎች በስድብ መንፈስ መሳደብ መብታቸው ነው። ሆኖም የሚሰድቡት ስም ጠቅሰው ከሆነ እነሱም ስማቸውን መጥቀስ ማለትም ቢቻል በፌስ ቡክ አካውንታቸው በመግባት አስተያየታቸውን መጻፍ ይገባቸዋል። Anonemous  ሆኖ  የስድብ ነገር አስተያየት መስጠት አይቻልም።

2. አኖኒመስ ሆኖ ስድብ የሚጽፈውን መብቱን ለማፈን ሳይሆን የሌላውን መብት ለመጠበቅ ጽሑፉን እንሰርዘዋለን።

3. በአንድ አከራካሪ ነጥቦች ላይ ሐሳብ ለምትሰጡ ግን ስማችሁን ደብቃችሁ ቢሆን አስተያየት (comment) መስጠት ትችላላችሁ።

በመጨረሻ ግን ክፉ በሆነ አንደበታቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች በመስደብ ራሳቸውን ሊቅና ፈራጅ ያደረጉትን ልብ ይስጥልን። 

No comments:

Post a Comment