Sunday, December 16, 2012

የስምዖን ዓምዳዊ ጸሎት (ክፍል አንድ)



ምዕራፍ ፩፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ በፊቴ የሕይወትን በር ክፈትልኝ። አንተ የሕይወትና የድኅነት በር ነህ፤ የሚያገኝህ በውስጣዊ ሰውነቱ ሕይወትን ያገኛል። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ንጹሑን የእግርህን ተረከዝ ታቅፈው ዘንድ፥ በእንባዋ ነጠብጣብ ታርሰው ዘንድ፥ ከእርሱም የሕይወትን መዓዛ ታሸት ዘንድ ለነፍሴ ስጣት። ለዓለማት ሕይወትን የምትሰጥ ፈውሰኝ፤ ፈቃድህን እንድፈጽም የበቃሁ አድርገኝ። የምትመግበኝ የአንተ ፈቃድ እንጂ የእኔ ፈቃድ አይሁን። ስለ እኛ በላከህ በአብ፥ ወደኛ ባወረደህ በፍቅርህ፥ ሥራዎችን ሁሉ በምታከናውንበትና በምትቀድስበት በመንፈስ ቅዱስ እለምንሃለሁ። ከአእምሮ በላይ በሆኑ ምሥጢራትህ  የተሞላ፥ ንጹህና ቅዱስ መቅደስህ እሆን ዘንድ፥ በነፍሴና በሥጋዬ፥ በልቡናዬና በሕሊናዬ ቅድስናን ስጠኝ፤በወለደችህ፥ በእመቤታችን ማርያም እለምንሃለሁ፤ በተሸከመችህ ማኅፀን፥ በተሸከሙህ ጉልበቶች፥ ባቀፉህ ክንዶችህ፥ ባጠቡህ ጡቶች፥ ለእኔም ለኃጢአተኛው መጋቢ ረዳትና ጠባቂ ሁን አሜን።

ምዕራፍ ፪፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የሚለምኑህን ተስፋቸውን የማታሳፍር፥ መምጣትህን ስለተነበዩ ስለነቢያት፥ ወንጌልህን ስለሰበኩ ስለሐዋርያት፥ በፊትህ ሥጦታ ሆኖ ተቀባይነት ስላገኘ ስለ ሰማዕታት ደም፥ በየገዳማቱና በየበዓታቱ ወድቀው ስላሉ አባቶች እንባ  እለምንሃለሁ፤ መሪዬ ሁነኝ፤ መንገዴን አቅናልኝ፤

ምዕራፍ ፫፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በማኅፀን የሠራኸኝ፤ መሪና አዳኝ ሁነኝ። 

1 comment: