Tuesday, December 25, 2012

ልብን የሚነካ የአብሮነት መግለጫ

በዚህ በአገረ አሜሪካ ከሚገኙት ታዋቂ የአሜሪካ ፉት ቦል ቡድኖች መካከል (ሶከሩን አይደለም) አንዱ ኮልት ነው። ታዲያ ከሰሞኑ የአሰልጣኙን በሉኪሚያ ካንሰር መታመም ተከትሎ ሠላሳ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች፥ የዋናውን አሰልጣኝ በኪሞ ቴራፒ ውስጥ ማለፍ ለማበረታት ጸጉራቸውን ተላጭተው ነበር። ከሁሉ ልቤን የነካው ሁለት የቡድኑ አድማቂ (cheerleaders) እህቶች አብረው ጸጉራቸውን መላጨታቸው ነው። ቅዱስ መጽሐፍ «ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚለቅሱም ጋር አልቅሱ።» ይህንን ታላቅ ድርጊት ደግሞ ራሱ ቤዛችንና መድኅናችን አድርጎታል። በኃጢአት ፍላጻ ተነድፎ ለሞት የተሰጠውን የሰው ልጅን ከወደቀበት ሐዘቅት ያድነው ዘንድ፥ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እኛን መስሎአል። የቤተ ክርስቲያን ጥሪዋና ድምጽዋ በውጭ ላሉት ሊደርስ ያልቻለው፥ እኛ « በውስጥ» ያለነው ብዙ ጊዜ የምንጨነቀው ራሳችን ከሌሎች ለመለየት እንጂ ከተጠቁት፥ ከተገፉት፥ ልባቸው ከተሰበረውና ግራ ከገባቸው ጋር አንድ ለማድረግ አይደለም። የኮልት ቡድን አባላት ድርጊት ታላቅ ትምህርት ያስተምረን ይሆን? 

No comments:

Post a Comment