Wednesday, May 22, 2013

መዝሙረ ዳዊት 9 ወይስ 10 ?



የእንግሊዘኛውን መዝሙረ ዳዊትና የአማርኛውን ወይም የግእዙን መዝሙረ ዳዊት ብትመለከቱ ወዲያው የምታስተውሉት ነገር ቢኖር፥ የምዕራፎቹ መለያየት ነው። ይህ የምዕራፎቹ መለያየት የሚጀምረው በመዝሙር 9 ላይ ነው። የግእዙና የአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ የግሪክኛውን የሰብዓ ሊቃናቱን ትርጉም አከፋፈል ተከትሎ መዝሙር ዘጠኝን በ38 ቁጥሮች ሲያስቀምጥ፥ የእንግሊዘኛዎቹ ትርጉሞች ግን (ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ትርጉሞች በስተቀር)  የዕብራይስጡን የማሶሬያቲክ ዘር ተከትለው መዝሙር ዘጠኝን ለሁለት ከፍለውት እናገኛለን።  አንዳንዶች ወገኖቻችን የዕብራይስጡ አከፋፈል ከፍ ያለ ክብር እንዳለው አድርገው ሊያሳዩን ይፈልጋሉ። ይህ ግን ልክ አይመስለኝም። እርግጥ ነው፥ መዝሙረ ዳዊት ከዕብራውያን ትውፊት የተገኘ ነው። ነገር ግን የማሶሬያቲክ ዘር ከክርስቶስ ልደት በኋላ በመቶዎቹ ዓመታት ዘግይቶ የተሰባሰበ ሲሆን የሰባ ሊቃናቱ ደግሞ ከክርስቶስ ልደት በፊት የሆነ ነው። ለምሳሌ መዝሙር ዘጠኝን ከተመለከትን የዕብራይስጡን ፊደል ተከትሎ የተጻፈ ስለሆነ ምዕራፍ ዘጠኝና አስር የሆነው መሐል ላይ ተከፍሎ ነው። በመሆኑም ብዙዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋ መተርጉማን መዝሙሩ አንድ ምዕራፍ እንደህነ ይስማሙበታል። ያም ሆነ ይህ የምዕራፉ ልዩነት በአማርኛ ለሚያነበውም ሆነ ከእንግሊዘኛው ጋር ለሚያገናዝበው ግራ ማጋባቱ እርግጥ ነው። ይህ የምዕራፍ ልዩነት የሚጀምረው ምዕራፍ 9 ላይ ይሁን እንጂ በየቦታው ልዩነት ስላለው ልዩነቱን ለመገንዘብ የሚከተሉትን ማየት መልካም ነው።  በእንግሊዘኛ ስናነብም ሆነ አንዳንድ በዲጂታል የተጻፉትን ስናነብ ይህን የምዕራፍ ልዩነት ልናስተውል ይገባል።

የግሪኩ አቆጣጠርየእብራይስጡ አቆጣጠር
1-81-8
99 and 10
10-11211-113
113114 and 115
114116:1-9
115116:10-19
116-145117-146
146147:1-11
147147:12-20
148-150148-150

No comments:

Post a Comment