Tuesday, March 5, 2013

ጸሎተ ስምዖን ዓምዳዊ ክፍል 9

ምዕራፍ ፳፭፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ የአንተን ደስታ ሙላብኝ። አንተ ሐዘን የማያገኘው ደስታ ነህና። በነፍሴ ውስጥ አገኘው ዘንድ ይህን ደስታ ስጠኝ። ነፍሴ ንጹህ ማደሪያና ምርጥ ዕቃ ትሁን። ልቤ ታቦትህ ሕሊናዬም ምሥዋዕ  ይሁንልህ። ብርሃናውያን የሆኑ የመላእክትህን ምስጋና ያሰማ። ልቡናዬ ከፍ ካለው የመላእክት የምስጋና ድምጽ ጋር ይዋሃድ። 
ምዕራፍ ፳፮፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ፍጥረትን በተሐድሶ አዲስ ለማድረግ የመጣህ፥ በምሕረትህ አድሰኝ። 
ምዕራፍ ፳፯፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ራስህን በዮሐንስ ፊት ዘንበል (ዝቅ) ያደረግህ፥ ለክብርህ በሚገባ ምስጋና ከፍ ከፍ አደርግህ ዘንድ፥ ኃጢአት ከብዶት ዘንበል ያለውን ራሴን ከፍ አድርግልኝ። 

No comments:

Post a Comment