Tuesday, June 5, 2012

የተቀበልነው ስጦታ 3:1-29



1. የእምነት በቂነት 3:1-5 
የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው? 2 ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ በሕግ ሥራ ወይም ከእምነት ጋር በሆነ መስማት መንፈስን ተቀበላችሁን? 3 እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን? 4 በውኑ ከንቱ እንደ ሆነስ እንደዚህ ያለ መከራ በከንቱ ተቀበላችሁን? 5 እንግዲህ መንፈስን የሚሰጣችሁ በእናንተም ዘንድ ተአምራት የሚያደርግ፥ በሕግ ሥራ ነውን ወይስ ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው?
1. የገላትያ ሰዎች የማያስተውሉ እንዲሆኑ በሌሎች ተጽዕኖ ሥር ወድቀዋል:: 
2. ባለማስተዋላቸው ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር መቃረን ጀምረዋል::  
3. ባለ ማስተዋላቸው በእነርሱ ውስጥ ያለውን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ መቃረን ጀምረዋል:: 
3.1 የክርስትናቸውን ጅማሬ ያገኙት በእምነት ከሆነ መስማት በሆነ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ነው:: ሮሜ 8:9:: 
3.2 መንፈስ ቅዱስ በመካከላቸው ሆኖ የሚሰራው ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው:: 
       ልጅነትን በማስረገጥ- ሮሜ8:15-16:: 
       ተአምራትን በማደረግ  
       ፍቅርንና የመንፈስ ፍሬዎችን በመስጠት 
4. ከእምነት በሚገኝ በመንፈስ ቅዱስ ከጀመራችሁ በሕግ ሥራ በሚገኝ በሥጋ አትፈጽሙ:: ሮሜ 8:13:: 
2. የአብርሃም ምሳሌነት 3:6-9
እንዲሁ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነና ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። 7 እንኪያስ ከእምነት የሆኑት እነዚህ የአብርሃም ልጆች እንደ ሆኑ እወቁ። 8 መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ። 9 እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።
1. አብርሃም ጽድቅን ያገኘው በእምነት ነው:: ዘፍ 15:6:: 
2. የአብርሃም የሆኑት ሁሉ የአብርሃምን ጽድቅ የሚያገኙት በአብርሃም እምነት በኩል ነው:: ዘፍ12:2
3. አብርሃምንና በእምነት ልጆቹ የሆኑትን አሕዛብን የሚያገናኛቸው ሁለቱም ያመኑበት ወንጌል ነው:: 
3.1 የአብርሃም ልጆች መሆን ለአይሁድ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የተሰጠ ነው:: 
3.2 የአብርሃም ልጆች መሆን አብርሃምን መምሰል ከእኛ የሚጠብቅ ነው:: ዮሐ 8:39::
3.3 የአብርሃም ልጆች መሆን ማለት የአብርሃምን በረከት ወራሾች መሆን ማለት ነው:: ገላ 3:29:: 
4. በእምነት የሚገኘው ጽድቅ በእግዚአብሔር ፊት ልጅነታችንን ለማግኘት መሰረት ነው:: 
4.1 ጽድቃችን የአብርሃም ልጆች በመሆናችን የምናገኘው ውርስ ነው:: ይህም የኃጢአትን ፍርሃት በማስወገድ እውነተኛ የሆነ ሕብረት ከእግዚአብሔር ጋር እንዲኖረን ያደርጋል:: 
4.2 ለቤዛ ቀን የሚያትመን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ የአብርሃም ልጆች በመሆናችን የምናገኘው ውርስ ነው:: ይህም የሞትን ፍርሃት የዘላለምን ሕይወት ተስፋ በማድረግ ይተካዋል:: 
3. ከሕግ እርግማን ነጻ መውጣት 3:10-14
ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፤ በሕግ መጽሐፍ በተጻፉት ሁሉ ጸንቶ የማይኖር የማያደርግም ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና። 11 ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው። 12 ሕግም ከእምነት አይደለም ነገር ግን። የሚያደርገው ይኖርበታል ተብሎአል። 13 በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤ 14 የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል፥ የአብርሃም በረከት ወደ አሕዛብ በኢየሱስ ክርስቶስ ይደርስላቸው ዘንድ።
1. ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸው:: 
2. ክርስቶስ ከሕግ እርግማን ዋጅቶናል:: 2 ቆሮ 5:21:: ኢሳ 53:4-6
3. ክርስቶስ ከሕግ እርግማን የዋጀን የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል ነው::  
4. ዘርና መካከለኛ የሆነው ክርስቶስ 3:15-22
ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። የሰው ስንኳ ቢሆን እርግጠኛውን ኪዳን ማንም አይንቅም ወይም አይጨምርበትም።16 ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር። ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን። ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ። 17 ይህንም እላለሁ፤ ከአራት መቶ ሠላሳ ዓመት በኋላ የተሰጠው ሕግ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተረጋገጠውን ኪዳን የተስፋውን ቃል እስኪሽር ድረስ አያፈርስም። 18 ርስቱ በሕግ ቢሆንስ እንግዲያስ በተስፋ ቃል አይሆንም፤ በተስፋ ቃል ግን እግዚአብሔር ለአብርሃም ሰጥቶአል።19 እንግዲህ ሕግ ምንድር ነው? ተስፋው የተሰጠው ዘር እስኪመጣ ድረስ በመካከለኛ እጅ በመላእክት በኩል ስለ ሕግ መተላለፍ ተጨመረ። 20 መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ግን አንድ ነው። 21 እንግዲህ ሕግ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል የሚቃወም ነውን? አይደለም። ሕያው ሊያደርግ የሚቻለው ሕግ ተሰጥቶ ቢሆንስ በእውነት ጽድቅ ከሕግ በሆነ ነበር፤ 22 ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ከማመን የሆነው የተስፋ ቃል ለሚያምኑ ይሰጥ ዘንድ መጽሐፍ ከኃጢአት በታች ሁሉን ዘግቶታል። 
1. ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው ተስፋ ዘላለማዊ ተስፋ ነው:: 
2. የአብርሃም ዘር የተባለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: 
3. ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠውን ተስፋ ከ430 ዓመት በኋላ የመጣው የሙሴ ሕግ አልሻረውም::
3.1 ሕጉ የተሰጠው ኃጢአትን ለመግለጥ ነው::ሮሜ 4:15::
3.2 ሕጉ የተሰጠው የኃጢአትን አስከፊነት በማሳየት ሰዎችን ወደ ጸጋ ለማድረስ ነው:: ሮሜ 5:20:: 

No comments:

Post a Comment