Tuesday, April 3, 2012

የጌታ ኢየሱስ ሕማም ሞትና ትንሣኤ የሉቃስ ወንጌል ዝርዝር ቢጋር ከሌሎቹ ወንጌላት ጋር በማነጻጸር (22:1-24:53)

ሀ. የመጨረሻዎቹ ሰዓታት (22:1-46)
1. 22:1-2 - የአይሁድ አለቆች ጌታን ለመያዝ ማሴራቸው::
(ማቴዎስ 26:6-13:: ማርቆስ 14: 3-9:: ሉቃስ 7:36-50:: ዮሐንስ 12:1-8:: ሽቱ መቀባቱ :: )
2. 22:3-6 - የይሁዳ ክህደት ( ማቴዎስ 26:14-16:: ማርቆስ 14:10-11:: ዮሐንስ 13:2,27,6:70)
3. 22:7-14 - የበዓለ ፋሲካ ዝግጅት :: ማቴ. 26:17-20:: ማር 1:12-17:: ዮሐ 13:1
( ዮሐንስ 13:1-20 ጌታ የደቀመዛሙርቱን እግር ማጠቡ:: )
4.22:15-20 የመጨረሻው ራት:: ማቴ 26:26-29:: ማር 14:22-25:: ዮሐንስ 6:51-58::
5. 22:21-23 - ስለ ይሁዳ ክህደት የተነገረ ትንቢት
6. 22:24-30 - የደቀ መዛሙርት ክርክር
( አዲሱ የፍቅር ትዕዛዝ ዮሐንስ 13:31-35::)
7. 22:31-34 - ስለ ጴጥሮስ ክህደት የተነገረ ትንቢት:: ማቴ 26-30-35:: ማር 14:26-31: ዮሐ 13-36-38::
22:35-38 - ስለ ዝግጅት
(የስንብት ንግግር በዮሐንስ ወንጌል )
ዮሐ 14:1-14:: << ልባችሁ አይደንግጥ>>
ዮሐ 14:15-26:: የመንፈስ ቅዱስ ተስፋ
ዮሐ 14: 27-31:: የሰላም ስጦታ
ዮሐ 15:1-8 ኢየሱስ እውነተኛው የወይን ግንድ
ዮሐ 15:9-17 በፍቅሬ ኑሩ::
ዮሐ 15:18-25 የዓለም ጥላቻ
ዮሐ 15:26-27 የመንፈስ ቅዱስ ምስክርነት
ዮሐ 16:1-4 ስለ ስደት
ዮሐ 16:5-15 የአጽናኑ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ
ዮሐ 16:16-22 ሐዘን ወደ ደስታ ስለመለወጡ::
ዮሐ 16:23-28 በኢየሱስ ስም ስለመጸለይ
ዮሐ 16:29-33 ስለ ደቀመዛሙርት ሽሽት ትንቢት
ዮሐ 17:1-26 የሊቀ ካህንነቱ የምልጃ ጸሎት

ለ. የጌታ ኢየሱስ መያዝና ፍርድ (22:39-23:25)
1. 22:39-46 - በጌቴሴማኒ መጸለዩ:: ማቴ 26-36-46:: ማር 14:32-42:: ዮሐ 18:1::
2. 22:47-53 - የኢየሱስ መያዝ:: ማቴ 26:47-56:: ማር 14:43-52:: ዮሐ 18:2-12::
3. 22:54-71 - ኢየሱስ በአይሁድ ሸንጎ ፊትና የጴጥሮስ ክህደት:: ማቴ 26:57-68:: ማር 14:53-65:: ዮሐ 18:13-24::
4. 23:1-2 - ኢየሱስ በጲላጦስ ፊት መቆሙ ማቴ 27:1-2:: ማር 15:1:: ዮሐ 18:28::
(ማቴ 27:3-10 የይሁዳ ሞት::)
5.23:2-5 - ኢየሱስ በጲላጦስ መመርመሩ:: ማቴ 27:11-14:: ማር 15:2-5:: ዮሐ 18:29-38::
6. 23:6-12 - ኢየሱስ በሔሮድስ ፊት
7. 23:13-16 - ጲላጦስ በጌታ ኢየሱስ ላይ ምንም ጥፋት አለማግኘቱ:: ዮሐ 18:38::
8. 23:17-23 - ኢየሱስ ወይስ በርባን:: ማቴ 27:15-23:: ማር 15: 17-23:: ዮሐ 18:39-40::
(ዮሐ 19:1-15 ጲላጦስ ጌታን መግረፉና ወታደሮች በጌታ በኢየሱስ ላይ መዘበታቸው:: )
23:24-25 - ጲላጦስ በጌታ ኢየሱስ ላይ የሞት ፍርድ መፍረዱ


ሐ. የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀል (23:26-56)
1. 23:26 - ስምዖን ቀሬናዊ መስቀሉን መሸከሙ:: ማቴ 27:31-32:: ማር 15:26-32:: ዮሐ 19:17::
2. 23:27-31 - ጌታ ኢየሱስ ለኢየሩሳሌም ሴቶች የተናገረው ቃል
3. 23:32-34 - የጌታ መሰቀል ማቴ 27:33-37:: ማር 15:22-26:: ዮሐ 17-27::
4. 23:35-38 - ጌታ በመስቀሉ ላይ እንደዘበቱበት:: ማቴ 27:38-43:: ማር 15:27-32
4. 23:39-43 - ኢየሱስ እና ሁለቱ ወንበዴዎች:: ማቴ27:44:: ማር 15:32:: ዮሐ 19:18
5. 23:44-48 - የኢየሱስ ሞት:: ማቴ 27:45-54:: ማር 15:33-39:: ዮሐ19:28-30::
6. 23:49 - የመስቀሉ ምስክሮች ማቴ 27:55-56:: ማር 15:40-41:: ዮሐ 19:25-27::
(ዮሐ 19:31-37:: የኢየሱስ ጎኑ መወጋቱ )
23:50-56 - የአርማትያሱ ዮሴፍ ጌታን መቅበሩ:: ማቴ 27:57-61:: ማር 15:42-47:: ዮሐ 19:38-42::
(ማቴ 27: 62-66 የአይሁድ አለቆች መቃብሩን በወታደሮች ማስጠበቃቸው )

መ .የጌታ ትንሣኤ (24:1-53)
1. 24:1-12 - ባዶው መቃብርና ሴቶች ማቴ 28:1-8:: ማር 16:1-8:: ዮሐ 20:1-13::
(ማቴ 28: 9:10:: ዮሐ 20:14-18 ጌታ ኢየሱስ ለሴቶቹ መገለጡ::
(ማቴ 28:11-15 የወታደሮቹ ሪፖርት
2. 24:13-35 - ጌታ ኢየሱስ በኤማውስ መንገድ ለሁለቱ ደቀመዛሙርት መገለጡ:: ማር 16:12-13::
3. 24:36-43 - ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ መገለጡ:: ማቴ 28:16-20:: ማር 16:14-18::ዮሐ 20:19-23
( ዮሐንስ 20:24-29:: ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ በሙሉ ዳግመኛ መገለጡ
(ዮሐንስ 21:1-14 በጥብርያዶስ ባህር ለደቀ ቀመዛሙርቱ መገለጡ::
4. 24:44-53 - የጌታ የመጨረሻ መመሪያ እና ዕርገቱ:: ማቴ 28:16-20:: ማር 16:9-20:: ዮሐ 21:14-25::